ሠላም ለሁላችሁ ይኹን!
ግንቦት 13 ቀን 2012 ዓ.ም
ዉድ ቤተሰቦቼ በጸሎት እየበረታችሁ እንደሆነ አልተጠራጠርኩም፤ ፈጣሪያችን ያበርታን
!
ከዳዊት መዝሙር የሚበልጥ ጸሎት እንደሌለ ተማምረናል ፤ የዛሬዋን እንሆ!
ጠዋት ስንነሳ ለጸሎት ሥንቆም ከዘወትር ጸሎታችን ቅድሚያ እነዚህ የዳዊት መዝሙራት
ይጸለያሉ መዝሙር 5 ፤ 56፤ 62
ማታ ከመተኛታችን በፊትም የሰላም ሌሊት እንዲያደርግልን ከመጸለያችን በፊት መዝሙር
140 ይጸለያል ፤
(ምስጢሩም ጠዋት 3 ማታ 1 ይሆናል)
የዛሬዉ ሁለተኛዉ መልዕክቴ በምሥጢር ስለተመላችዉ ስለ ሃገራችን ኢትዮጵያ ይሆናል
!
ኢትዮጵያ ሃገራችንን
ወደ ቀደመ ክብሯ እና ለዛዋ ይመልስልን !
ማንኛዉም መፍትሔ ያለዉ ከቤተክርስቲያናችን መሆኑን የቀደሙ ነገስታት ጠንቅቀዉ ያዉቃሉ
፤ ስለሆነም ምክር ይጠይቋታል እርሷም ትሰጣቸዋለች፤ መፍትሔዉም ከእግዚአብሔር ተቀብላ ስለሰጠቻቸዉ ያማረ የሰመረ ነበር፤ አሁንም
ፓርላማዉ ያለ እርሷ የሚያዋጣ አይሆንም፤ እንዲህ ሕዝቡን የሚያፋጀዉ ቤተ ክርስቲያንን በማስወገዳችን ነዉ፤ ሕጉን ከዳሰሰችዉ የቀና
ይሆናል ፤ አሁንም ትግባና ታስተካክለዉ ፤ ቀብታ ያነገሰቻቸዉ ነገስታትን ጸሎት በእንተ ንጉሥ ብላ ትጸልይላቸዉ ነበር፤ አሁን ግን
ይኽ ጸሎት ቢኖርም ንጉሱ የለም፤ ቅብዓ-ነገሥቱም ቀርቷል፤ የቅብዓ-ነገሥቱ ብልቃጥ ግምጃ ቤት ተቀምጦ ይጮኻል ! ! !
የነገሥታት አምላካቸዉ ወደ ነበረን ክብራችን ይመልሰን ፤ አሜን + + +
No comments:
Post a Comment