Wednesday, August 25, 2021

ስለ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያዉያን አንደበት !

 ሰላም ለኩልክሙ !

 ዘመነ ማቴዎስ ወርሃ ነሐሴ መዓልቱ 17 ሌሊቱ 10 ጨረቃዉ 16

 ሳናስተዉለዉ የምንኖረዉን እንዳንኖረዉ !

 የኢትዮጵያ የዘር ሐረግ 4 ግንዶች የተገኘ ነዉ፤ አሪት ዘፍጥረት 918

. ነገደ ኦሪት

. ነገደ ካም

. ነገደ ሴም

. ነገደ እስራኤል

 . ነገደ ኦሪት ከእስያ ተነስተዉ መጥተዉ 2256 እስከ 1030 . 1226 ዓመት በኢትዮጵያ ነግሠዉ ነበር፤ በኖኅ ዉሃ ጥፋት ተደመሰሱ፡፡

. ነገደ ካም ሦስት ነገዶች ሲሆኑ ነገደ ሻንቅላ ነገደ ቅማንት፣ ነገደ ወይጦ እና ነገደ ሽናሻ ናቸዉ ሁሉም የካም ልጅ ከነዓን ልጆች ናቸዉ፡፡ የቅማንቶች አባት አይነር የካም ልጅ የከነዓን የልጅ ልጅ ነዉ፡፡ሚስቱ እንተላ ትባላለች፡፡

. ነገደ ሴም (ነገደ ዮቅጣን) ሴም 15 ልጆችን ወለደ 3ኛዉ አርፋክስድ ይባላል፤ አርፋክስድ ዓቦር ፋሌክንና ዮቅጣንን ወለደ፣ ዮቅጣን 13 ልጆችን ወለደ አንዱ ሳባ ነዉ፤ የሳባ የልጅ ልጁ ኢትዮጲስ ይባላል ከኢትዮጲስ ኢትዮጵያ ተባለች፤

ኢትዮጲስ 5 ልጆችን ወለደ እነሱም

1. ላክንዱ -

2. ሳባ - ትግሬዎች

3. ኖባ - ጎጃም ነጭ አባይ እና ጥቁር ዓባይ ያለበት

4. በለዉ - ሰግላና ሐማሴን ኤርትራዉያን

5. ከለዉ - አማራ ወልቃይት ጠገዴ

የኢትዮጵያ ዋና ባላባቶች 6 ናቸዉ አማራ (ወልቃይት ጠገዴ ጎጃም ጎንደር ሸዋ) ትግሬ አገዉ በደዉ አስገዴ ብቅላ ሐባብ ናቸዉ 

በደዉ(ኤርትራ የሚገኙ ብሌኖች) አስገዴ ብቅላ(ሐረር ድሬዳዋ የሚገኙ) እና ሐባብ(አፋር እና ሱማሌ የሚገኙ) ከወንድሞቻቸዉ ተለይተዉ በእስልምና ሃይማኖት ገብተዉ ልዩ ወገኖች ሆነዋል ሌላዉ ሕዝብ ከእነዚህ ሲዋለድ የተገኜ ነዉ፡፡

. ነገደ እስራኤል ከቀዳማዊ ሚኒሊክ ጋር ታቦተ ጽዮንን ጽላተ ሙሴን አጅበዉ የመጡ ሲሆን በብዛት በጎንደር አካባቢ የሚኖሩ እና ከሌሎቹ ነገዶች በተለየ ፈላሲ(ፈላሻ) የተሰደዱ በመባል ይታወቃሉ፤ በእደ ጥበብ እና ቅርሳቅርስ ስራዎች የታወቁ የተደነቁ ናቸዉ፡፡

 ጋሎች ከእስያ መጥተዉ በገላኔ ወንዝ አካባቢ ሆር ዉላቦ በሚባል ቦታ ሰፈሩ አባቶቻቸዉ በርቱማ እና ቦረን የተባሉ ወንድማሞች ናቸዉ፤ በርቱማ 6 ቦረን 11 ልጆች ወለዱ፤ ፍጥረት ከዉሃ መጣ በማለት ለዉሃ ይሰግዳሉ፤ ብዙ ከብት ፍየል በግ ያርዳሉ ዉሃዉን ግን አይቀምሱም፡፡

327 . በአጼ ዐምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት በትግሬ ጉርዓ ከሚባል ኣገር ከኩሎ ግዛይ ክፍል የወጣ ሠራዊት ከአዝማች ስብሓት ጋር መጥቶ በአይመለል ተሠራ፡፡ ስለዚያም ኣገር እና ሕዝብ ጉርዓጌ ተባለ፡፡

በኢትዮጵያ የገቡ እስላሞች 4 ዓይነት ናቸዉ፤ 1 ሕምሪያ (ቀይ) 2 ትግሬ(ነጋዴ) 3ኛ፡ አርጎቦች 4ኛ፡ በመሃመድ ጊዜ ተሰደዉ የመጡት ናቸዉ፡፡

 ታሪክ ማወቅ ሁሉም ከአንድ አዳም እና ሔዋን ዘር ከኖኅ ከእስያ እንደፈለሰ ስለሚያስረዳ የኔ ሳይሆን የእኛ ሃገር ብሎ ተከባብሮ ይኖራል፤

 ሁሉም ወደ ማዕከለ ምድር ኢየሩሳሌም ይመለከታል ሁሉም በዓለም ተበትኖ የሚኖር የማዕከለ ምድር የኤልዳ ዉጤት ነዉ፤ ሁሉም ከመሬት ከእሳት ከዉሃ ከነፋስ የተፈጠረ የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት ነዉ፤ የመጣበትን አለማወቁ ግን ሁሌም እርስ በእርስ ሲያጠፋፋዉ እና ሲያገዳድለዉ ኑር የተባለዉን ዕድሜ ሳይኖር ሲሸኛኝ እንመለከተዋለን፤ የዕዉቀት ማነስ ከሁሉም የሚበልጥ ድኅነት ነዉ፤ ፈጣሪ ማስተዋሉን ያድለን አሜን + + +







ምንጭ አለቃ ታዬ የኢትዮጵያ ታሪክ ክብረ ነገስት ገጽ 40 እስከ 50 ኤር 387 ፤መዝ 6830 ዘፍ 918 ሐዋ 836 ሶፎ 310

No comments:

Post a Comment