ሰላም ለኩልክሙ !
ነሐሴ
15 ቀን 2012 ዓ.ም
የድንግል ማርያም ስጋ እንዲነሳ እና እንዲያርግ ምክንያት የሆነበት !
አንድ
ክርስቲያን ሊያዉቃቸዉ ግድ የሆኑ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ነገሮች ፤( ነገረ ክርስቶስ )!
ከቤታችን
በትልቁ ጽፈን ልንሰቅለዉ የሚገባ ፤ ስንወጣ ስንገባ ልናየዉ ልናስተምረዉ የሚገባ ግዴታችን!
የሃይማኖታችን
መሰረት ፤ በዚህ ዉስጥ ቅድስት ሥላሴ፤ ቅድስት ድንግል ማርያም እና ቅዱሳን ያሉበት መደምደያ ነዉ!
9 ዓቢይ
በዓላት
1.
ትስብዕት - ሰዉ የሆነበት
የ40 ቀን ጽንስ ሆኖ በድንግል ማኅጸን የተገኘበት መጋቢት 29
2.
ልደት - በቤተልሔም
በበረት የተወለደበት ሰዎች ሳይዉቁት እንስሳት እስትንፋሳቸዉን ያሞቁበት ታህሳስ 29
3.
ጥምቀት - ዮር እና ዳኖስ ፤ ሰማይና ምድር፤ ሰዉና መላዕክት አንድ የሆኑበት ዉሃ
የተቀደሰበት ክርስትና የተወለደበት ጥር 11
4.
ደብረ ታቦር - ሰዉ ብቻ አለመሆኑ
የታወቀበት መለኮቱን በትንሹ ያሳየበት እንደየደረጃቸዉ ምስጢር የገለጸበት ነሐሴ 13
5.
ሆሳዕና - የአህያን ታዛዥነትን ያወደሰበት፤ ንጉስነቱን ለሕጻናት የገለጸበት ፤ድንጋይን
ያናገረበት ከትንሳኤ በፊት ያለዉ እሑድ
6.
ስቅለት - በመስቀል ዙፋኑ የነገሰበት፤ መስቀልን በደሙ አትቶ ለመድኃኒትነት የሰጠበት፤
ሲኦልን ባዶ ያደረገበት አርብ
7.
ትንሣኤ - የሰዉን ስጋ አምላክ
ያደረገበት ፤ መቃብርን ያሸነፈበት ፤ ደስታን ለዘለዓለም የሰጠበት እሑድ
8.
ዕርገት - የሰዉ ስጋን ወደሰማይ ያወጣበት ፤ ምድር ጊዜአዊ መሆኗን ያረጋገጠበት ከትንሳኤ በአርባኛዉ ቀን ያለች ሀሙስ
9.
ጰራቅሊጦስ- ለሰዉ ልጅ ጥበብን
የሚሰጥ መንፈስቅዱስን የላከበት ፤ አንድነት ሦስትነት የተረጋገጠበት ከትንሳኤ በሃምሳኛዉ ቀን
1.
መስቀል - የወንበዴዎች መቅጫ
ወደ መድኃኒትነት የተለወጠበት መስከረም 17
2. ስብከት - ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል እያሉ የተነበዩበት መታሰቢያ ታህሳስ 7
3.
ብርሃን - ክርስቶስ በብርሃን እየተመሰለ የሚነገርበት ታህሳስ 14
4.
ኖላዊ - ክርስቶስ እዉነተኛ እረኛ መሆኑን የሚዘገብበት ታህሳስ 21
5.
ጌና - የክርስቶስ ልደት በ4 ዓመት አንድ ጊዜ የሚከበርበት ዐማኑኤል ተብሎ ይከበራል
ታህሳስ 28
6.
ግዝረት - ግዝረት ሳይፈጸምለት
ተገዝሮ መገኘቱ የሚከበርበት ጥር 6
7.
ቃና ዘገሊላ - በሰርግ ቤት
የመጀመሪያዉን ተዓምር ዉሃዉን ወደወይን የቀየረበት ጥር 12
8.
ልደተ ስምዖን - ስምዖን አረጋዊ
ለ300 ዓመት ሳይሞት ቆይቶ ጌታን ያየበት የታቀፈበት በዓል የካቲት 8
9.
ደብረ ዘይት - የጌታችን ነገረ
ምጽአት የሚነገርበት የዐቢይ ጾም አምስተኛዉ እሁድ (እኩሌታ)
1.
ተአስሮ ድኅሪት - ወደኋላ
አጥንቱ እስኪገጥም መታሰር
2.
ተቀሥፎ ዘባን - ጀርባዉን
መገረፍ
3.
ተኮርዖ ርእስ - ራሱን መመታት
4.
ወሪቀ ምራቅ - ምራቅ በገጹ
ላይ መትፋታቸዉ
5.
አክሊለ ሦክ - የእሾህ አክሊል
6.
ፀዊረ መስቀል - መስቀል መሸከም
7.
ተጸፍኦ መልታሕት - ጉንጭ
መመታት
8.
ሰትየ ሐሞት - ሐሞት መጠጣት
9.
ቅንዋት ዘየማን እድ - የቀኝ
እጅ መቸንከር
10.
ቅንዋት ዘጸጋም እድ - የግራ
እጅ መቸንከር
11.
ቅንዋት ዘየማን እግር - የቀኝ
እግር መቸንከር
12.
ቅንዋት ዘጸጋም እግር - የግራ
እግር መቸንከር
13.
ዘእንግዳ ቀኖት - የደረት
መቸንከር
ተዘከርዎ
ለክርስቶስ ወሰናያቲሁ ኢትርስኡ - ክርስቶስን አስቡት ያደረገዉን መልካም ነገርም አትርሱ !
ሃገራችን
በሰማይ ነዉ ፤ ደግ እንሁን ፤ በተስፋ እንኑር፤ መልካሙን ብቻ እናስብ፤ ክፉ ከአፋችን እንዳይዎጣ ምላሳችን እንቆጣጠረዉ፤ በየቀኑ
ምን ያህል መልካም ነገር ተናገርኩ ብለን ራሳችንን እንጠይቀዉ፤ አምላካችን በሰማይ በደስታ እንድንኖር ያድርገን ፤ የእመቤታችን
ድንግል ማርያምን ትንሳኤ ሃዋርያት እንዳዩ ሃገራችንን ትንሳኤዋን ያሳየን ፤አሜን ! ! !
No comments:
Post a Comment